Friday, September 12, 2014

ዘመነ ሉቃስ ይህ አብይ ጥያቄ ይዞ ቀርቧል! ዜግነት ወይስ ዲሞክራሲ?





Getachew Reda (Editor Ethiopian Semay)
ከኢትዮጵያን ሰማይ ድረገጽ አዘጋጅ መልዕክት September 11/ 2014 (Meskerem 2007 Ethiopian New Year)
በመጀመሪያ በርካታ እጅግ ፤እጅግ፤እጅግ ከጠበቅኩት በላይ በርከታ የድጋፍ እና የማበረታቻ ደብዳቤዎች እና አዲስ አመት አንኳን አደረስህ ብላችሁ ለላካችሁልኝ ወዳጆቼ በሙሉ ከልቤ አጅግ በጣም አድርጌ አመሰግናለሁ። ደብዳቤዎቻችሁ በጣም በርካታ ስለሆኑ በደፈናው ስማችሁን ከመጥራት ይልቅ ወዳጀቼ ብዬ በመጥራት አመሰግናችሗለሁ። ለናንተም አንኳን አደረሳችሁ። ጊዜ በማጣት መልስ ያልጻፍኩላችሁ ወዳጆቼ በዚህ አጋጣሚ አንደገና መልስ  እንደምጽፍላችሁ ለማሳወቅ እወዳለሁ። አመሰግናለሁ።በዚህ አጋጣሚ የሚጨሁላቸው አጥተው በባዕድ አገር ተጠልለው ወያኔ አፍኖ ሊወስዳቸው ሲጥር ድምፅ ሆኜ እየጮህኩኝ ከዛ ከጨለማ ቦታ አውጥቼ ወደ አሜሪካ አገር እንዲመጡ የረዳሗቸው ወገኖች እዚህ ከመጡ በሗላ “በአውዳመት ጊዜ” አንኳን አደረስህ ለማለት የነፈጉኝ በመከራ ጊዜያቸው የደረስኩላቸው ወገኖች በዚህ ዓለም መኖሬን ቢረሱትም ፤ብዙ ወዳጆች በማፍራቴ በነሱ ላይ አይዞህ ባይነት “ድምፅ” እጽናናለሁ፡ እና እነሱን ለአንባቢ ለትዝብት ሰጥቼ ልለፋቸው። 



ዘመነ ሉቃስ ይህ አብይ ጥያቄ ይዞ ቀርቧል!

ዜግነት ወይስ ዲሞክራሲ?
ጌታቸው ረዳ



ለ23 አመት የቆረቆዘው ተቃዋሚ በተለይ ከአማራ ነገድ የተወለደው “ቡሃቃ” የአማራ ልሂቅ የገዛ ወላጆቹ በባንዳዎች ክብሩ ሲነጠቅ፤ ሲዋረድ እና የሕግ ያለሕ፤የረዳት ያለህ እያለ የተማረውን ወገኑን አንዲያድነው የአማራ ሕብረተሰብ በጩኸት እየተማጸነ እንዲደርስለት በጩኸት ቢማጸንም “ጆሮው ደፍኖ” አልሰማ በማለት ከተጃጃለው ተቃዋሚ አብሮ ሲደልቅ ይኼው ወገኖቹ ለጥቃት ተዳርገዋል።

ሊንኩን በተለጠፈው ቪዲዮ እንደምታዩት፣ አንድ ሕዝብ አማራ በመሆኑ ብቻ ሀብት ንብረቱን ተቀምቶ ይፈናቀላል። አዲስ አመት ጊዜውን ጠብቆ ይመጣል፣ አዲስ ትውልድም ይተካል፣ በትግራይ ብሄረተኞች የምትፈጠረዋ የነገዋ ኢትዮጵያ ምን ልትመስል እንደምትችል ግን ቆም ብለን ማሰብ ይኖርብናል።

የቆረቆዘው ተቃዋሚ እንቁጣጣሹን ይህንን አሳዛኝ ገመናው እየተመለከተ እንዲያሳልፈው እራሱን በመስተዋት አንዲያይ ይረዳው አንደሆን ይኼው አዲሱን አመት በዚህ አብይ  ጥያቄ አንድ በሎ ጀምሯል። ይህን አሳዛኝ ገመና የተቀረጸ ቪዲዮ አንዲመለከቱ አዲሱ አመት ጋብዞዎታል። የቢራ ሰአትዎ አንዳይሻማ አጠር ብሎ የተቀረጸ ነው። Amhara farmers in southern Ethiopia cry for justice   


 

Getachew Reda (Editor Ethiopian Semay)