Monday, July 23, 2012

በሽተኛው መለስና በሽተኛው ስርዓቱ፤ የሰሞኑን ውሎየን ላወያያችሁ።

Meles Zenawi of TPLF drafting a plan how to destroy Ethiopia to establish Tigray Republic

በሽተኛው መለስና በሽተኛው ስርዓቱ፤ የሰሞኑን ውሎየን ላወያያችሁ።


ጌታቸው ረዳ (ኢትዮጵያን ሰማይ)


ለመልእክት አስተያየት getachre@aol.com

ሰላም እንደምን አላችሁ። እኔን የማንበብ ልምድ ያላችሁ ቅዱሳን ወገኖቼ ለቅዱስ ዮሓንስ የሚደርስ አዲስ መጽሐፍ እየጻፍኩ ስለሆነ በየጊዜው ካላነበባችሁኝ ይቅር በሉኝ፤አደራ።

መለስ ሞቷል፤ ታሟል የሚለው ዓለም አነጋግሯል። መለስ ባይሞትም መለስ መጥፎ ነውና ከመልካም የታሪክ ሕሊና ከሞተ ብዙ ቆይቷል። መለስ መጥፎ ብቻ ሳይሆን፤ጠማማ፤ መሰሪ (የውጭ ልኡክ)፤ኢትዮጵያን የማውቅ እና ኢትዮጵያን የሚጠላ (ወያኔው ብስራት አማረ በሃዋርያ ጋዜጣ ጽፎ የነገረን) የወያኔዎች መሪ ነው። መጥፎ መሪ የአንድ አገር የወደፊት ዕድል ብቻ ሳይሆን የሚያበላሸው፤የሕዝቡ ሞራል እና ባሕልም ጭምር ነው።

እዚሁ በምንኖርባት አገር አሜሪካ እንኳ መጥፎ መሪዎቻ ከጠንካራና ሃብታም አገር ወደ ከሰረች አገር መርተው የወደፊት ዕጣ ፈንታዋን አበላሽተውባታል። የመንግሥት ስልጣን ከያዙት ትልልቅ መሪዎች ጀምሮ እስከ “ዎል ሰትሪት” ተብሎ ከሚታወቀው ዓለም አቀፍ የባንክ፤ የንግድ መልህቅና ማእከል የሚመሩ መሪዎች አገሪቷን ከኩሩ እና አበዳሪነት ወደ “ተበዳሪ እና ኮስማና ባዶ ኪስነት/ቺስታ”(ባንክራብት) ወለል አውርደው የአገሪቱ የትምህርት፤የጤና፤የእርሻ እና የመገናኛ አውታሮች በመንቀሳቀሻ ገንዘብ እጥረት ምክንያት ሠራተኞችን  በማሰናበት እንዲዘጉ አድርገዋል። ይህ አሳዘኝ ክስተት የመሪዎች መጥፎ አመራር እና የመሪዎች በትክክል ባለማሰብ፤የገንዘብ እና የሃብት፤የሥልጣን አልጠግብ ባይነት የሕሊና መቀቃዋስ ያመጣው ውጤት ነው።

ናምንም ባናምንም መቀበል የሚያስገድደን ሁኔታ፤ በእንደዚህ ዓይነት የፖለቲካ፤የመንግስት እና ተራራ የሚያክሉ የንግድ ተቋማት ገብተው በመምራት ላይ የነበሩና ያሉት ኩሯን አገር ወደ ተመጽዋች እና ወደ ፍርክስክስነት (ክራይስ) ከሚመሩ ጎዶሎ መሪዎች እና ያለ መሪ ሕይወትን መምራት ብናነፃጽረው ምንም ለውጥ የለውም።

እንደዚህ ዓይነት መጥፎ መሪዎች መላዋን ዓለም ሞልተዋታል።በዛው አንፃር የሕዝቦች ኑሮ ተቃውሶ ጭለማ ሕይወት እንዲመሩ ተገዷል። አገራችን ኢትዮጵያ “ኩሩ” ተብለው ከሚጠሩ አገሮች ምናልባትም በቅድሚያ የምትወሳ አገር ነች።እርግጥ ኩራቷ ለሕሊና ቀውስተኞች አይስማማም። ልብ ብሎ በሰከነ ሕሊና የአገሪቷ ታሪክ፤ሕይውት እና ውስብስብ መሰናክሎች በዘዴና በመጋፈጥ አልፋ ራሷን አሁን ወደ አለችበት እርከን ለብዙ ሺሕ አመታት እንዴት እንደጠበቀች ላሰላ ሰው አስገራሚ እና ኩሩ አገር መሆኗን ይደመድማል።

የኮራች ኢትዮጵያ የሚል መዓረግ ሲሰሙ “ትግርኛን መጻፍ አግዳ አማርኛ እንዳውቅ በግድ አስተማረቺኝ” ስለዚህ ኩራቷ ገደል ይግባ” የሚሉ የጣሊያን ቡችሎች ተበራክተዋል። አገር በስሜት የሚገነባ በስሜት እንደ ጭቃ የሚፈርስ የሚመስላቸው አሻንጉሊቶች እንደ አሸን ፈልተዋል። ይህ ሁሉ የሕዝብ ባሕል እና ሞራል መላሸቅ ተጠያቂዎቹ እንደ መሰል ዜናዊ የመሳሰሉ የኮሞኒሰት እና የፋሺስት ብሄር ብሐረሰብ….ልክፍት አቀንቃኞች የሚያላዝኑ ሕሙማን መሪዎች እንደሆኑ መሰመር አለበት።

አገር ሕዝብ ነው፤ብዙ ባህሪ የያዘ አስፈሪና አዳጋች ደን ነው። የብዙ ሕዝብ ባሕሪ ለመምራት ጤነኛ የመንፈስ የስነምግባር እና አገራዊ ፍቅር መታጠቅ መለኪያው ነው።”ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ” ብሎ ራሱን የሚጠራ “ትግራይ ነፃ አውጪ” ድርጅት ከመነሻው ሲነሳ አነሳሱ የትግራይን ችግር ለመቅረፍ በሚል ነው የተደራጀው እና ተዋግቶ “በለስ ቀንቶት” የመንግስትን መንበር የነጠቀው። ወደ ስልጣን ሲሸጋገር ኢትዮጵያዊነት ሕሊናው አልነበረውም እና ዘርፎ አድበስብሶ “ትግራይን በልማት” ገንብቶ አንቀጽ 39ን በመጠቀም ትግራይን ገንጥሎ ጠላት በሚላቸው አማራዎች (ጎንደር ጎጃም ወሎ፤ ምናልባትም አፋሮች) እና ነፃ አገር ንነ ብለው “አጋሜ” ብለው በሚሰድቡን ኤርትራዊያኖች ተከብቦ “የአክሱም የእንቅልፍ ዘምን” ተከናንቦ ሕዝቡን ‘ፓራያ’ (የቁም እስር መንግስት ለማድረግ ነው።

ያንን ከማድረጉ በፊት ግን መለስ ዜናዊ በተጠናወተው በሽታ አገሪቷን በየዛው የጎሳ በሽታ በክሎ ፍርክስክሷን ለማውጣት እቅዱ እየተሳካለት ነው። ነገር ግን ብዙ ይቀረዋል። ያንን የመጨረሻው ዝርፍያን እና አገሪቷን ወደ አመድነት የመቀየር ሁኔታ ሳያጠናቅቅ ሲሰቃይበት ከነበረው የጎሳ በሽታ ከእግዚሃር የተላከበት በባሰ በሽታ ተይዞ ወደ በልጅየም ሄዶ  በሚሊዮኖች የሚቆጠር የኢትዮጵያ ገንዘብ ወጪ በማድረግ ከሞት ለመዳን “ውጪ ነብሲ ግቢ ነብሲ” ጣረሞት ውስጥ እንዳለ አውቀናል።

የዚህ ከንቱ ግለሰብ ጤና ብዙዎቻችን “ይዞህ ይሂድ” ስንል ወያኔዎች ግን “ተንቀጥቅጠዋል”። ከመንቀጥቀጥ አልፎ ተናደዋል። “ይዞህ ይሂድ” ያሉትን እየኮነኑ ያለ የሌለ ስድብ በማውረድ “ኢትዮጵያዊነት ባሕሪ ያልተላበሱ፤ ርሕሩህ ልብ የጎደላቸው” ሲሉ ጩሆታቸውን አሰምተዋል። ባለፈው ሰሞን የአሜሪካ ድምፅ የአማርኛው ክፍል የድሮ የወያኔ መስራች እና መሪ የነበረው አቶ ግደይ ዘርአጽዮንን በመጋበዝ ስለ መለስ መታመም አስመልክቶ አስተያየቱን እንዲሰጥ እንዳደመጣችሁት ተስፋ አለኝ። በወቅቱ አቶ ግደይ ዘርአጽዮን የመለስ መታመም ሲተነትን መለስ በያዘው በሽታ እግዚሃር ቢያሰወግደው ለአገራችን ሕዝብ የሚበጅ እንደሆነ አስተያየቱን ሲገልጽ፡ ወያኔዎች ግን ኩፉኛ በመቆጣት “ዓይጋ ፎረም” በተባለው የወያኔዎች ድረገጽ የሚከተለው ብሎ ነበር::
  

Comment on Gidey’s remarks on PM Meles’ health!
Zeru Hagos July 20, 2012-- The secret behind TPLF’ssuccess is one and simple. The organization simply trusted the people to nurture and defend it against its adversaries. And boy did they!...On hindsight it seems that not all TPLFites knew this secret! The latest news about PM Meles’health has opened a window for many Diaspora talking heads to spew their venomous hateful analysis on the air. One among them is Gidey Zeratsion...”

በማለት የመነጋገሪያ መድረክ በመክፍት ወያኔዎች መለስ ዜናዊ በሞት አፋፍ በመገኘቱ ድንገተኛ “ርሕሩሕ ልብ፤ሰብአዊነትን የተላበሰ ኢትዮጵያዊ አዛኝነት” ተላብሰው ግደይ ዘርአጽዮንን “ኤርትራዊ እንጂ ኢትዮጵያዊ አይደለም፤ በማለት ኤርትራዊነቱን በመጠቆም ኤርትራዊ ባህልና ልብ እንጂ ርህሩሕ የሆነው ኢትዮጵያዊነት ያልተላበሰ….” በማለት በጣም አስቀያሚ እና ጎሰኛ/ዘረኛ ባህሪያቸው አንጸባርቀዋል። እኔ እና ግደይ አብረን በአንድ ከተማ ያደግን ብንሆንም እና ካየሁት የቆየ ቢሆንም ኢትዮጵያዊ እንጂ ኤርትራዊ ዜጋ ነኝ ብሎ አያውቅም። ወያኔዎች ግደይን በዚህ መወንጀላቸው በጣም አስቀያሚ የሆነ ምልክታቸው የሆነ ዘረኝነትን አንጸባርቀዋል።
መለስ ቢሞት ደስታውን አንችለውም “በዛው ይዞት ይሂድ!” ስለተባለ አንዳንዶቹ በዚህ ተቆጥተው “አንቀጽ 39 የተባለው የፋሺስቶች እና የኮሚኒሰት መርሆ አንቀጽን በመጥቀስ “ትግራይ ሪፑብሊክን” አንመሰርታለን በማለት አስቂኝ እና ማስፈራሪያ የህፃን ቁጣቸውን አሰምተዋል። ከዚያ ሁሉ የሕጻን ቁጣቸው ይልቁንስ ያስገረመኝ “የወያኔ ጀሌዎች” በሰው ልጆች ላይ “ሞትን አትመኙ” በማለት ኢትዮጵያዊ ሰብአዊነትን ተላብሰው “ድንገተኛ ሰብአዊ ርህራሄ” አቀንቃኞች መሆናቸውን ሳነብ እጅግ ነው የገረመኝ። ለዚህ ሁሉ የመለስ እርግማን ደግሞ ተጠያቂ ያደረጉት፤መለስ ዜናዊ እና ካድሬዎቹ በአእምሮአቸው ውስጥ የከተቱባቸው የማመካኛ ጎዳናቸው የሆነው የፈረደበት “አማራውን” ነው። እዛው ከመድረኩ የተሰነዘሩት አስተያየቶች ታገኟቸዋላችሁ።
 እዛው መድረክ ገብቼ ከነዚህ “በድንገት፡ ወደ ሰብአዊነት ወደተለወጡት የወያኔ ጅሎች እና ጀሌዎች ጋር ለመነጋር ገብቼ ነበር። ከመለስ ጀሌዎች የሚሰነዘረው አስተያት እና ቁጣ በጣም አስገራሚ ነው። የድረገጹ አዘጋጅ “Uncivilized and Unlike any Ethiopian!” የሚለው ለግደይ የተሰነዘረው ርእስ ሳነብብ ድንገት የተደቀነብኝ ነገር “እነዚህ ሰዎች አርቆ አሳቢነት እና ኢትዮጵያዊነት፤ለሰው ልጅ አዛኝነት የሚባሉት በጎ ስነምግባሮች አሁን እንዴት ተገለጸለቸው?” ነበር ያልኩት። ይህ ከመከሰቱ በፊት  እውነት እንዚህ ሰዎች ለማንኛውም ኢትዮጵያዊ እና ተቃዋሚ ሰው ሲሞት እና ሲታመም አዛኞች ነበሩ ይህ ጉዳይ ሳንሸፋፍን መነጋገር አለብን።  አልነበሩም። እነዚህ ሰዎች እና የፖለቲካ ድርጅታቸው እጅግ በተወሰነ የድርጅት ፍቅር እና ክልል እይታ የታጠሩ ርህራሄ የሌላቸው እጅግ ጠባብ እና ለተወሰነ ሕዝብ ብቻ የሚያዝኑ እና የሚቆረቆሩ ናቸው።
ታስታውሱ እንደሆነ እዛው በመላው ዓለም ውስጥ የተበተኑት ትግሬዎች ተሰባስበው ቴሌ ቶን’ በመባል የሚታወቀው የመሰባሰቢያ ጥሪ በማድረግ በወቅቱ 9.6 ሚሊዮን ሕዝብ በረሃብ ተሰቃይቶ የወያኔ መንግስት የልመና ኮሮጆ ዘርግቶ ሹሟሙንቶቹ አሰማርቶ በየዓለማቱ ለማስመሰያ ሲለምን (ለዘርፊያም ሊሆን ይችላል) በሌላ ጎኑ ደግሞ የትግራይ ተወላጆች ለትግራይ ትምህርት ቤቶች መገንቢያ ሲያሰበሳስቡ ነበር። ይህ የምታስታውሱ ብዙዎች ናችሁ የሚል ግምት አለኝ።
በዛች አንድ ቀን በተደረገው የገንዘብ መዋጮ 60 ትምህርት ቤቶች የሚያሳንፅ ገንዘብ በማሰባሰብ “ሰብዓዊ ሕሊና እና ኢትዮጵያዊነት ቸርነት” ጥለውት እንደነበር የምታስታውሱት እንደሆነ ተስፋ አለኝ። በዛው ወቅት ከዘጠኝ ሚሊዮን ሕዝብ በላይ ለተራበ ሕዝብ እና በረሃብ በበሽታ ሲሞት ፤ሕጻናት በእናቶቻቸው ክንድ ለዘላለሙ አሸልበው ሲያልፉ፤እናቶች በሃዘን ተወግቶ አምባቸው ሲያወርዱ፤ትግራይ ግን ረሃብ ተወግዶ፤ ለትግራይ ሕዝብ ልጆች ለትምህርት ቤት ማስገንቢያ የሚሯሯጥ ለትግራይ ሕዝብ ልቡ ተንጠልጥሎ የሚንገበገብ፤ አሁን ድንገት በመለስ ዜናዊ በሽታ እና ስቃይ “አልቅሱ፤ ተጨነቁ” እያሉ መለስን ያወገዙትን “ኢትዮጵያዊነት-ያልተላበሰ-ልብ”-ሲሉ-ገርሞኝ-በፎሮሙ http://aigaforum.com/blog1/2012/07/21/uncivilized-and-unlike-any-ethiopian/comment-page-2/#comments ላይ ሰሞኑን የጻፉትን የሰጠሁት መልስ ላስነብባችሁ።

Do you remember the “Tigrayan telethon” a campaign to collect money for Tigray school constructions? Do you remember the event? Do you remember what was taking place in Ethiopia particularly in the Eastern part of our country Ethiopia? Let me put it in short to remind your memory “incase”. The event that Telethon was conducting was a period of terrible starvation taking place by millions in the eastern and Amhara region as well.

The Eritrean Hilawe Yosef on Behalf of the people who he said represents Amhara ethnic (as if he or his family born Amhara)  contributed $2,000,000 for school in Tembiyen Awaraja  money snached from the starved and unemployed Amhara farmer, He donated the money for Tigrayan because Hilawe said it is a “payback” for they supported ADM during the struggle (literally for hiring them as a puppet to steal money from the Amahara society,and live lavish and as TPLF's Amharic Department).

The other contributor was a government branch called “Ethiopian Electric Power” which donate money to built 2 schools in Tigray (remember at this moment when the event is taking place, millions were starving, the world is in a hot perused of contribution to help the starved in Ethiopia).


The next was Ethiopian Telecommunication donated huge sum of money to built several schools in Tigray.

The other contributor was . Ministry of Ethiopian defense (department of Industries/engineering) contributed huge sum of money for MatChew Awraja in Wereda “MoKoni” to build a preparatory school.

Many numbers of Tigre individuals contributed by millions and hundreds of thousands in single contribution. To mention the few;- Ato Selama Gebru (100,000ብር) (this fellow lives in Nazret and made his fortune in Nazret- unfortunately his son died and said "my son is dead, from now the replacement for my son are the Tigray children and will donate one fully facillitated school in Adi Aferom village and aslo money for a road constraction in that village. He (in other words the kids in Nazret are not his replacment kids, but the Tigrayan kids. Now figure that out, how narrow nationalism is dangerous!!!) 

The next contributers was TPLF member Mr. Alamoudi who donated money for being baptized by the TPLF Ambassador Tewelde Ageme and Assefa Mamo as a pay back for baptizing him to be TPLF member, Mahber LimAt Tigray, ……..many of them in massive and  each of them contributed huge sum of money. To the extent money to built 1 and 2 schools (this is from individual donation). Let me remind you again, 9.6 Million Ethiopoan was starved at that moment when this Tele tone was running.

The point that you need to take a note of it is – that, we the Diaspora opposition and Ethiopian citizens were contributing money for the starved people. Our representatives went to Ethiopia with our contribution with the knowledge of Ethiopian government/TPLF government agreement just to give access for them to donate it to the starved people. It was a tense and repressive momment for patriotic nationalist Ethiopians to hear a starvation again while these TPLF tycoons are sending money to Tigray for school constraxtion. All the TPLF Ministers/officials were all over the world begging for donation to help the starved while Telethon was held for school construction in Tigray!!! At one day- money was collected enough to built 60 new schools in Tigray!!

Note;- The starvation the hunger was bad and broadcasted by german radio and VOA Amharic programs. At that week one dry Enjera was $3.oo that was sold $1.25. some people on VOA and German radio told $10.00 ብር.

Mr. Gezaee tell us your memory, if such is fair, when Ethiopian Electric power corporation (there was power frailer in Addis remember!? it was called LIGHT BEFEREKA) and other government agencies involved in such from its badget and employees and was sending money for Tigray Scool constraction while the people starved, while we the Diaspora also sending money for starved people in Ethiopia from here. Where was the heart of these new “HUMANITARIANS of MELES ZENAWI’s at that time?

This telethon campaign was held in Sheraton Addis in a city where millions of homeless and starved people live where few coraupt individuals and exploiters dance and enjoyed., and where the starved lower government workers and others eat once or twice a day and code was given to it "11 and 5" (no breakfast in the morning you eat if "possible" your lunch and breakfast at 11 and eat your dinner at 11 Alamoudi was thanking TPLF Tewelde Agame of TDA for baptizing him as TPLF for for the first time by coming to his house and allowing his capital to invest his money in Ethiopia. He donated huge money for his Tigray to glorify TPLF. At that moment children and domestic animals (camel, cows….) were dying (evidence was on TV throughout the world) in the Eastern part and some areas as well.

It was the corrupt and narrow nationalist "Iyasu Berhe" (the singer who passed away last year) leading the Telethon. Many of those Tigrayan are milliners who made their investment in Nazret and Amhara and other regions, but they were building school for Tigray not for Nazret or Harar. Ogaden where millions were starved in that week. Is it fair? This telethon campaign was held in Sheraton Addis in a city where millions of homeless and starved people live. Where was your Ethiopiawinet heart at the time? Now you have the nerve to attack Gidey or anyone for wishing Meles’s death?

በማለት ነበር ሊሸሽጉት የሞከሩትን  ያደፈውን መስተዋታቸውን አውጥተው እንዲመለከቱት የጠየቅኳቸው። ቀጥየም ስለ ማሕበር ተጋሩ ሰሜን አሜሪካ የሚባለው በቅንጅት መሪዎች ላይ ያስተላለፈውን ለመለስ ዜናዊ የጻፉትን ደብዳቤ በጨረፍታ እንዲህ ስል አስታወስኳቸው።

“Those who of you who now are sorry for Meles Zenawis ailment and felt as if you have humanity to all human being is a fake so to speak. If indeed those are crying with sympathy too much for Meles Zenawi should have shown similar sympathy to those TPLF/Meles victims as the result whom some are dead and disappeared and some are crippled and their life destabilizedsome languishing in known and unknown horrible prison cells.

Are not those same elements who wrote a letter of appeal to their Prime Minister to execute opposition “extremists” /the terminology that should belong to TPLF) with “YEMAYADAGIM IRMIJA” Do you know who they are? They are members of the “UTNA” (Union Tigrayan in North America), now this like members and individuals are trying to attacking Gidey ZeraTsion for his personal view (because Gidey similarly labeled Meles Zenawi worst extremist individual and wish him to go away for good).

 How is that the TPLF sympathizers have all rights to seek death to the opposition with the “YemaYadagim Irmija”, but not Gidey when it comes to wish Meles’s God’s YemaYadagim Irmija ordered by God? They are telling Gidey to be polite to all human creation/ You mean to tell us all in a sudden TPLFiets are now coming with Human face after their leader is caught by God’s power?

If you are now wearing human heart and felt humanity to all humans, then what I want TPLF followers to do is not what Meles Zenawi’s admirer Gezaee.H is advocating like the following


(I think Meles Zenawi is doing a good job lately. TPLF has to implement the article 39 now. So that people can live in peace in their respective region becoming countries. They have aleady called Tigray. Let it be Tigray republic now.” Gezaee H. July 21, 2012 at 2:04 pm Aigaforum discussionforum,)
I was not shock by such silly elements. But, I said, nstead what I am asking you all is the following if you are for human rights and kind heart as you all TPLF followers are now demanding from Gidey ZerAsion and others,  the opposition to change. Here is what I said about change and kindness that you primary need to do first before demanding change of heart from the opposition towards your leader Meles Zenawi;-

“If change to come and vengeance to replace by Christian concept of pardoning the sinner- the abuser in power have to admit he sinned and asked for forgiveness in detail what he did as a sinner without reasons of walls or barbed wire or armed guards to hide from the eye of the people/justice. Mr.Gezaee.H – I want to tell you this- I am not for bloodshed or vengeance but will speak out for the rights of my people . If you are asking people to change – you take the role of being reconciler and that is to urge your leader to establish special prosecution for TPLF victims. Change will come immediately.”

 ይህ ነበር የሳምነቱ ውሎየ ባጭሩ።የሞሶለኒ ተወካይ ግራዚያኒ ኢትዮጵያን ሲረግጥ ሲያበጣብጥ አንድ ሰሞን ወሬው ሲሰወር’ እርጉሙ ግራዚያኒ ሞተ፤ተጠለፈ፤ታመመ፤ የት ሄደ? አረ በዚያው ይዞት ይሂድ! ብለው ሲመኙ እና ሲጠይቁ “ግራዚያኒን ወድደውት ሳይሆን ያችን የናፈቋትን ነፃነት ከማስተንፈስ አኳያ ነበር።  አሁንም መለስ ዜናዊ የት ሄደ? ሞተ? ጠፋ፤ታመመ፤ታሰረ፤ ምን ነካው?  አረ በዛው ይዞት ይሂድ! ብለው ሲሉ እና ሲጠቁ  የግራዚያኒን ታሪክ እና ሁኔታ ስላስታወሳቸው መሆኑን ልብ በሉ። መጥፎ መሪ የአንድ አገር የወደፊት ዕድል ብቻ ሳይሆን የሚያበላሸው፤የሕዝቡ ሞራል እና ባሕልም ጭምር ነው፡ያልኩበት ምክንያትም ከዚህ አኳያ ነው።

ሕዝቡ ሲራብ የመለስ ተከታዮች ስለ ትግራይ ትምህርት ግምባታ ገንዘብ ሲያዋጡ የሕዝቡ ሞራል እና ባሕል፤ አርቆ የመመለክት ክብደታቸው አበላሽቶታል። ስለዚህ ብዙ ሰዎች የመለስን መወገድ የሚመኙት ለኢትዮጵያ ወጣቶች እና ለሕዝቡ ሞራል እና ባሕል መበላሸት ተጠያቂው ብልሹው እና ጠማማው መለስ ዜናዊ ስለሆነ ነው።

“ስለ ኢትዮጵያ የሚያስብ ሁሉ በሰላም ይክረም” ነው ያለው የ“ቀለበትዬን ስጧት” ደራሲ ወንድሜ በልጅግ አሊ!  ሓምሌ 2004 ዓ.ም  ለመለስ አልሆነችም እና ክረምቱን ይከርማል ብላችሁ ነው? ወንድሞቼ ሁሉም የእግዚሃር ጥበብ ነውና “ይዞሕ ይሂድ” ከመባል ያድነን።

ወንድሜ አበበ ገላውም “መለስ ዜናዊን አስደንግጠህ ለክፉ በሽታ ጣልክብን ተብለህ ከመከሰስ ያድንህ። ድሮም ያልኩህ ይኼው ነበር፤ እንኳን አዳራሹ ላይ አልሞተብህ። ከዚያ ወዲያ ግን ጠበቃ መፈለጉ ለኛ ቀላል ነው። አስደንግጠህ በልጄም የሚባል ሀገር እንዲሄድ ማድረግህ ግን ያገሪቱን ገንዘብ እንዲባክን ምክንያት ሆነሃል; ቢሆንም ይቀር ብለነሃል; ገንዘብ የታባቱ!”
 ”በልጅግ እንዳለው በሉ ደህና እንክረም። ጌታቸው ረዳ (አትዮጵያን ሰማይ ብሎግ አዘጋጅ) www.ethiopiansemay.blogspot.com