Tuesday, April 17, 2012

ኢሳት ቴ/ቪዥን “ፓን” ኦሮሚያ እና “ፓን” ኢትየጵያዊነትን ማምታታቱን ያቁም!

Amhara Children slaughtered by Oromo Liberation Front in Ethiopia
Any books written by Getachew Reda can be purchased by contacting the following addresses. Getachew Reda P.O.Box 2219 San Jsoe CA 95109  getachre@aol.com (408) 561-4836 www.ethiopiansemay.blogspot.com

በመጀመሪያ ዜና
ኢሳያስን ከሚቃወሙ ወያኔ ከሚረዳቸው ከኤርትራ ብሄረተኛ ተቃዋሚ ድርጅቶች መካከል ውስጥ (ምንቅስቓስ ሓርነት ኩናማ) “የኩናማ አርነት እንቅስቃሴ” የተባለው ሽምቅ ተዋጊ ድርጅት መሪ የሆነው አቶ ቀርነሌዎስ ዑስማን  ስለ ድርጅቱ ጉዳይ የሰጠው ቃለ መጠይቅ አምና የተካሄደ ቢሆንም ዛሬም እንደ አዲስ በድጋሚ የሚከተሉት ነጥቦች ለኩናማ ድርጅት መመስረት ምክንያት ናቸው ያላቸውን በትግርኛ የሰጠው ቃለ መጠይቅ እንዲህ በማለት ገልጿል።
1ኛ ለኩናማ ብሄረሰብ ወደ በረሃ መውጣት እና የኢሳያስ መንግስትን ለመፋለም ከማንኛቸውም ጉዳት እና ጭቆና በበለጠ ዋናው የመነሻ ምክንያት የሆነን “በሃይለስላሴ ጊዜ እና በደርግ ዘመን ከአማራ እና ከኦሮሞ የወለዱ ኩናማዎች ከተወለዱ ልጆቻቸው ጋር “ንህ ኤርትራኖች አይደላችሁም” ተብለው ወደ ኢትዮጵያ እንዲባረሩ ካደረገ በሗላ የኩናማ ሕዝብ ኩፉኛ ስላስቆጣውና ቁጣውም በጣም ሰፍቶ ኩናማ አለበት በተባለው መንደርና ቤተሰብ ቁጣው ስለቀሰቀሰ “በዚህ ቁጣ ምክንያት”  በገዛ አገራቸው እና መሬታቸው እህቶቻችን እና ልጆቻችን ውጡ ብሎ ከነልጆቻቸው ያባረረልንን ዘረኛው ኢሳያስ አፈወርቅ እና አማካሪዎቹን በጠመንጃ መፋለም አለብን ብለን ወደ በረሃ ወጥተን “ይህ ድርጅት እንዲመሰረት ምክንያት የሆነን ይህ  የኢሳያስ ግልጽ ዘረኛ ጥቃት ነው” ብሎ አሰና ለተባለው የኤርትራ ተቃዋሚ ራዲዮ ጣቢያ ጋዜጠኛ በቃለ ምልልሱ አረጋጠ።

2ኛ- ከዚህም አያይዞ ጀብሃ እና ሻዕቢያ የተባሉት ሁለት የኤርትራ ታጣቂ ሽምቅ ተዋጊዎች የኩናማን ማሕበረሰብ በንቀት ተመልክተው ኩናማ ኤርትራዊ አይደለም እያሉ ማሕበረሰቡን ሲገድሉና ንብረቱን ሲነጥቁት እንዲሁም ሲያባርሩት፤ የኢትዮጵያ መንግስት የሃይለስላሴም ይሁን የደርግ መንግስት ግን ለኩናማ ሕልውና ተንከባክበውት እንደነበርና፤ ለሁለቱም ኤርትራ ድርጅቶችች ላይ ግን ማለትም በሻዕቢያ እና በጀብሃ ቅሬታው፤ ወቀሳውንና ምሬቱን ሳይደብቅ ተናግሯል።
3ኛ - ለድርጀቱ ህልውና የቆመለት “መሰሪው” ወያነ ትግራይ ቡድን በገንዘብ ስለሚረዳው ወያኔ ያስተማረውን የመገንጠል ፖለቲካ ተበድሮ “እስከ መገንጠል” የሚለው የስታሊን ኮሚኒስቶች ፖለቲካ ይከተላል።  አመሰግናለሁ። ጌታቸው ረዳ  (ኢትዮጵያን ሰማይ አዘጋጅ)።
ኢሳት ቴ/ቪዥን “ፓን” ኦሮሚያ እና “ፓን” ኢትየጵያዊነትን ማምታታቱን ያቁም!
ESAT TV “Stop being media for OLF Outlate” (www.Ethiopiansemay.blogstop.com) getachrre@aol.com
ከኢትዮጵያ ሰማይ አዘጋጅ ለኢትዮጵያ አገር ወዳድ ሃይሎች ማሳሰብ የምፈልገው ጉዳይ ኢሳት የተባለው የቴሌቮዥን ጣቢያ በተከታታይ ያለ ማቋረጥ ኦነግ ለተባለው ጸረ ኢትዮጵያ እና ጸረ አማራ የሆነ ወንጀለኛ እና አሸባሪ ድርጅት ኦሮሚያ ሪፑብሊክ ለመፍጠር፤ የኦነጉ ታሪክ ምሁር ተብየው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሟቹ አገር ወዳዱ የፕሮፌሰር አለሜ እሸቴ ተማሪ የነበረው “መሐመድ ሃሰን”  በ “The –Development of Oromo Nationalism" in "Being and becoming Oromo" edited by P.T. W Baxter, Sandro Triulzi and Jan Hultin, Uppsala 1996” በሚለው ለዶክተሬትነቱ የመመረቂያ ርካሽ ፕሮፓጋንዳ ጽሑፉ ላይ  በአማራዎች እና በትግሬ ኮሎኒያሊስቶች ጭቆና የተወለደ ኦሮሞነት ለማሳደግ  “ፓን ኦሮሞ ኮንሸስ” (Oromo conciouse, sense of national identity…” የማንንት መገለጫ የሆኑት “የኬኒያ ቦረና ኦሮሞዎች የሚጽፉበት “ቁቤ” የተባለ የአውሮጳ ፊደል” “የኦሮሞዎች ብሔራዊ የማንንት መለያ ባንዴራ፤ባሀል፤ስሜት፤ድምበር…..) ለማሳደግ ዩኒቨርሲቲዎች/አንትሮፖለጂስቶች እና ሚዲያዎችን ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ለማያውቅ  ሕበረተሰብ ማሳወቅ እና “ከኢትዮጵያኒስቶች” ጋር በሚዲያ ማሳደግ የሚለውን ትንቢታዊ እቅዱን ዛሬ  እንዳጋጣሚ ሆኖለት “ኢሳት”የተባለው “ቲቪ” የኦነግን ፕሮፓጋንዳ በማራገብ  “ፓን ኦሮሞ ኮንሸስ” (Oromo conciouse, sense of national identity…” የሚባሉትን የኦነግ መቀስቀሻ እሴቶች የሚባሉት ማለትም “ባንዴራዎቻቸውን፤ሙዚቃዎቻቸውን፤በራሪ ጽሑፎቻቸውን እና ንግግሮቻቸውን” ያለ ምንም ሳንሱር/ገደብ  ለአይናችን እስከሚያስጠላ እና እስከሚያቅለሸከልሸን ድረስ ለእኛ ለኢትዮጵያዊያን ባዕድ የሆነ የኦነግ ብንዴራ “በኢሳት ቴሌቪዥን” ሆን ተብሎ እየተውለበለበ  ለኦነግ የሰንደቃላማ ማስተዋወቂያ የቅስቀሳ ፍጆታ በመዋሉ፤ “ወያኔን ለመቃዋም” በሚል  “ከዚህም ከዚያም” የተጠረቃቀሙ “የአገራዊ ሰንደቃላማ ክብር ምንነት በቅጡ ያልገባቸው”  “ነፃ አገልጋይ” የጣቢያው ወጣት ተለማማጅ ጋዜጠኞች  የአገራችን የኢትዮጵያን ሰንደቃላማ ክብር የሚያወርድ ስራ በመስራት “የኦሮሞ ናሺናሊዝም” ማጎልበቻ የሚባለው አንዱ የሆነውን “ባንዴራቸውን እና መለያቸውን” እያውለበለቡ ያገራችን ሰንደቅ የሚያደርግና የሚያናንቅ ስራ በመስራት ላይ ናቸው። ይህ ድርጊት የተፈጸመው ከዚያ በፊት በተደጋጋሚም ሆነ አስመራ የመሸገው “ከማል ገልቹ” የተባለው የኦነግ መሪ ሰሞኑን ለቃለ መጠይቅ በጋበዘበት የተፈጸመ ባሳት ቲቪ ላይ የተፈጸመ ድርጊት ነው።
 ይህ የኢሳት ቲቪ “ጸረ ሉአላዊነት” ይህ ተደጋጋሚ ተግባር እንደተከናወነ በሰፊው ከነማስረጃው አስደግፈው ምሁሩ ክቡር ዶ/ር ማንከልክሎት ሃይለስላሴ ባለፈው ሰሞን ባለ ሦስት ተከታታይ ክፍል ያለው ጽሑፍ ለሕዝብ ያስተላለፉት በኢትዮ-ላዮን እና በአሲምባ ድረ ገጽ ላይ  የተለጠፈ ቢሆንም “የኢሳት የቲቪ” ባለቤቶች/ስራ አስኪያከጆች የዶክተር ማንከልክሎት ሃይለስላሴ ምክር እና ማስገንዘቢያ በንቀት ስላዩት ሴራቸውን አሁንም ቀጥለውበታል። አንባቢዎቼ ልብ እንድትሉት የምፈልገው “ኢሳት ቲቪን” በሚመለከት የዶ/ር ማንከለክሎት ሃይለስላሴ ጽሑፍ “ከወያኔ ሚዲያ የተሻልን ነፃ ሚዲያዎች ነን፤ ሃሳቦች በነፃ እናስተላልፋለን፤ የሚሉ የውሸት ሚዲያዎች፤  በተግባር ግን “ከወያኔ ሳንሱር የማይሻሉ” የተቃዋሚዎች ድረገጾች ለሕዝብ እንዲነበብ ለጥፉልኝ ብለው ቢልኩላቸውም  “ነፃ ፕሬስ ነን” የሚሉት እነኚህ “ወገንተኞች ሚዲያዎች” አፍነው አስቀርተውታል። ነፃ ሚዲያ ብሎ እንዲህም የለ!!!!!
 በበደኖ አርባ ጉጉ እና በተለያዩ ቦታዎች  የአማራን ሕብረተሰብ እና እናቶች እንዲሁም ህጽፃናት፤መነኮሳት እና ካሕናት ሲታረዱ ስትውለበለብ የነበረቺው የጠባብ ጐሰኛው የኦነግ ባንዴራ መሆኗን “ኢሳቶች” ቢያወቁም በተጠቀሰው የኢሳት ቴ/ቪዥን ጣቢያ ባለቤቶች በተደጋጋሚ ሆን ብለው በቴክኒካዊ አሰራር በስዕለ ድምፁ ገጽታ ላይ (እስክሪኑ ላይ) አንዴ ወደ ተመልካች ዓይን አስጠግተው በትልቁ እንድናየው አንዴ በርቀት፤ ኦነግ ባንዴራ አንዴ ከከማል ገልቹ ፎቶ ግራፍ ጋር ለጥፈው  አንዴ ባንዴራውን ብቻውን በማስጠጋት/ በማድመቅ እና በማስራቅ  “በሞሺን ግራፊክ/ፎቶ አኒመሽን” “እስኪያቅለሸልሸን ድረስ” አማራ ሲጨፈጨፍ በኩራትና በደስታ ስትውለበለብ የነበረቺው “የጠላት ባንዴራ”  የኢትዮጵያን ሕዝብ ሕሊና እና ዓይን በተለይም የኦሮሞን ማሕበረሰብ ሕሊና “ለመስለብና ለመሳብ”  “ንጉሥ ከሰማይ ይወርዳል” የሚለው ዳዊት የተባለው ውዥምብራም “የኦነግ ወጣት ዘፋኝ” የሚዘፍነውን ሙዚቃ ጆሯችን በማደንቆር እንድንመለከትላቸው በመቀስቀስ ዘመቻውን  አጧጥፎላቸዋል።  “ኢሳት”  በዚህ ሴራ መሳተፉን ካላቆመ  አገር ውስጥ  ያለው የኢትዮጵያ ሕዝብ “እንዲያወግዘው የኢትዮጵያ ሰማይ አዘጋጅ “ጥሪውን” በጥብቅ ያስተላልፋል።
ኢሳት የተባለው ሚዲያ ድሮ ብርሃኑ ነጋ እና ተስፋየ ገብረአብ እንደ የፖለቲካ አማካሪ ወይንም ትችት ሰጪዎች አድርገዋቸው እጅ እጅ እስኪለን ድረስ እየጋበዙ ሲያስደምጡን እንደነበር ይታወሳል። ዛሬ ደግሞ ብርሃኑ ነጋንና ተስፋየ ገብረአብ በኦነጉ ከማል ገልቹ የፖለቲካ ተንታኝ ተክተው በተደጋጋሚ በመጋበዝ “አማራ ሕብረተሰብ ከደቡብ አካባቢ ስለ መባረር ጉዳይ” በሚመለከት ስለ አማራ ሕብረተሰብ “ሞረሽ” ብሎ መደራጀት እና አለመደራጀት፤ እንዲተነትንልን  መጠየቃቸው ይገርማል። አማራው ለሌላ አላማ እስካልተደራጀ ጊዜ ቢደራጅ ምንም ችግር የለውም” አለው ከማል ገልቹ። “ለሌላ አለማ” ስትል ምን ማለትህ ነው? ብሎ እንኳ ጋዜጠኛው ተመልሶ አልጠየቀውም። አማራው ተደራጅቶ “ ኦነግን እና ወያኔን እንዲሁም በአማራው እና በዚህ ዓለም በምናኔ ባሉት ቅዱሳት መነኮሳት ላይ የዘመቱ ጂሃዲስት አክራሪ እስልምና ሰባኪዎች’ በዓለም ፍርድ ቤቶች “ክስ እስካልመሰረቱ ድረስ” ቢደራጁ ችግር የለውም ማለትህ ነው ብሎ ቢጠይቀውስ ምን አለው? ከዚህ ሌላ አማራው ምን አለማ አለው ብሎ ይገምታል? እንደ ኦነግ እንዳይገነጠል? ወይ ጉድ!
Pregnant Amhara woman slaughtered by OLF on the Genocide crime on Bedeno
“(እኔ አማራ አይደለሁም) “ለባለቤቱ” ለአማራው ጠይቀህ መልስ አግኝ”፤ብሎታል (ጥሩ አደረገ)። እናቴ ጥሩ ምሳሌ ተናጋሪ እንደነበረች ደጋግሜ ነግሬአችሗለሁ። “ደረቐኛ አንጭዋስ ብወጋሕታ ናብ ድሙ ከይዳ መሕብየይ ጉድጓድ በዚኣ ዶስ በዚኣ? ኢላ እንተጠየቐታስ “ ድሙኳስ በቲ ድርቅናኣ ተደሚማ/ገሪሙዋስ “ዋእ! ማዓረይ ዳሓንዶ!? “ታይ ዝብልዎ ጋዓት  ዲኺ ተደሪርኪ?” በለታ ይባሃል” ። ( ደረቀኛ አይጥ በጥዋት ገስግሳ የምደበቅበትን መከላከያ ጉድጓድ በዚህ ወይስ በዚህ ብቆፍር ይሻላል? ብላ ድመቲቱ ቤት ሄዳ አማካሪኝ ስትላት፤ “ድመቲቱም በደፋርነቷ ደንግጣ “ዋእ! የኔ ቆንጆ፤ ምክር ለማግኘት አንኳክተሽ የገባሽበት ቤት አውቀሺዋል? እንዲህ ያለ ድፍረት የሰጠሽ ምን እሚሉት ገንፎ በልተሽ ነበር ያደርሺው? አለቻት ይባላል)።  እንዲህ አይነት የሞኞች ዘመን በአገራችን ተስምቶ አይታወቅም? ስለ አማራ ራሱን ለመከላከል ስለ መደራጀት የህልውና ጉዳይ ከኦነጐች ምክርና አስተያየት መጠየቅ አስገራሚ ዘመን ነው።
Tekle-and-Mesay ESAT TV Journalist
አማራ ራሱን ለመከላከል የሚያስችል ብቃት፤ ኣባል፤ ገንዘብ፤ ሃሳብ፤ ጥበብ ካለው እና ማሰባሰብ ከቻለ ይደራጅ እላለሁ። እስካሁን ድረስ በበቂ ተደራጅቶ የተከላከለለት ማንኛውም  ስለ ኢትዮጵያ የቆመ ድርጅት/ፖለቲካ ስብስብ፤ግለሰቦች፤ግለሰብ  ደካማነት ስላሳየ እና አማራውን ከጭፍጨፋ መከላከል ስላልቻለ እና ከተጨፈጨፈና ከተባረረም በሗላ በዓለም ፍርድ ቤቶች ወንጀለኞችን ለፍርድ አቅርቦ ያስቀጣ ድርጅት ከ20 አመት በላይ ተጨባጭ ተግባር ስላልታየ፤ ስለ አማራው መከላከል እና ቁጭት “ከኢንተርኔት የቁጭት ንዴት ጽሑፍ” አልፎ ትግሉ ወደ ሕግ መድረክ ተሸጋግሮ ሕጋዊ ትግል እንዲያደርግ ራሱን ማደራጀት እና “መደራጀት አለበት”እላለሁ። አጋጣሚ መደራጀት የለበትም  ከሚሉት “በቅርብ የማደንቃቸው ካንዳንድ የትግል ወንድሞቼ ጋር በሃሳብ እለያለሁ”። ወንጀለኞች አሁንም ውጭ አገር ተቀምጠው ንቀታቸውን ከመቀጠል ሌላ ኢሳት ላይም ቢሆን ባንዴራቸው እያውለበለቡ ማላገጡን ቀጥለውበታል እና አማራ ራሱን መደራጀት እና ወንጀለኞቹን ከስሶ ማስቀጣት ይጀምር። ጠበቃዎች ይቅጠር፤ገንዘብ መዋጮ ይጠይቅ፤ ቀልዱ ይቁም!
ወጣት ጋዜጠኛው ኦነግ ስለ አማራ መደራጀት በጐነትና ጐጂነት ለምን እንደጠየቀው አሁንም በጣም ይገርመኛል። አማራው ተደራጅቶ ኖሮ ቢሆን ዛሬ  “የኦነግ ግመል እና የወያኔዎች በሬ” ሆኖ ለእርድ ይቀርብ ነበር? እንደ ጡበት በግ የአማራ ህፃናት ልጆቹ በቢላዋ የሚያርድ ኦነግ የተባለው እርኩስ የአረመኔዎች ድርጅት አማራ እንዲደራጅ እና ራሱን ከኦነግ እና ከወያኔ ጥቃት እንዲከላከል ፍላጎት ይፈልጋል ተብሎ ይገመታል?  ከማል ገልቹ ደጋግሞ ለምስኪኑ ጋዜጠኛው ለመሳይ ከበደ በምላሱ ደጋግሞ በቃለ መጠይቁ እንደተናገረው ድርጅቱ “የኦሮሞ ነፃነት አውጪ ግምባር” እያለ እንጂ “የኢትዮጵያ ነፃ አውጪ ግምባር” እያለ እንዳልተናገረ እያወቀና ከባንዴራው መለያ እና ከሚጠቀመው የራሱ ብሔራዊ ቋንቋ (አረብኛ እና ላቲን በሚጽፍ ቁቤ በሚባል ኦሮሚፋ/ኛ) ያለው “ኦነግ ሪፑብሊክ” የተባለ “የማናውቀው የአገር ባንዴራ ” የሚወክል መሆኑን ያረጋገጠለት ቢሆንም ምስኪኑ ጋዜጠኛ “ኦነግ”  “ኢትዮጵያዊነትን አቅፏል” ብሎ ቅዠት ላይ ገብቷል።
የጣቢያው ችግር ይገባኛል። “ተገንጣዮች ሳይቀሩ ማለትም ኦነጐች እና የኦጋዴን ነፃ አውጪ ድርጅት ኢሳትን በገንዘብ እና በፕሮፓጋንዳ ስለረዱት (እንደረዱ እራሳቸው ባስተላለፉት ዜና ዘግበውታል)   እንዲሁም ለኢሳት መዋጪ ሲጠየቅ የየራሳቸው ፖለቲካ ለማናፈስ ያመች ዘንድ  በአዳራሹ ዘንድ ሄደው በአካል ተገኝተው “ኢሳት ይዳብር” ብለው መርቀው ለምርቃታቸው ነፃ ፕሮፓጋንዳ ከነ ባንዴራቸው እንዲውለበለብ ተደርጓል።
ጣቢያው ለምሳሌ በቃለ መጠይቅ መልክ “የፖለቲካ እንግዶችን” በመጋበዝ በማይወዷቸው የፖለቲካ መሪዎች እና ድርጅቶች ሳይቀር “ስድብ” ሁሉ በማስተላለፍ ጣቢያው ይጠቀሙበታል። ለምሳሌ የግንቦት 7 ደጋፊ/አመራር የሆነው ዶ/ር ሸዋ ቀና የተባለው ሰው “በመ ኢ አ ዱ” ሃይሉ ሻውል ላይ ያነጣጠረው የስድብና የዘለፋ  ውርጅብኝ ያለ ምንም ገደብ እና ሳንሱር ወደ ኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲተላለፈ እንዳደረጉ የምታስታውሱት ሃቅ ነው። ይሄ ዓይን ያወጣ  ወገንተኛነት ነው። የሕዝብ ጣቢያ ነው እያሉ የጣቢያው ሰዎች የግል ጥላቻቸውንና ግባቸውን ግን ያስተጋቡበታል። ብርሃኑ ነጋ እና የጦቢያው  ሙሉጌታ የኦነጉ ሌንጮ (በሚኒሊክ እና በኢትዮጵያ እንዲሁም በአማራ) እና ሌሎች እንደዚሁም  በሃይሉ ሻውል እና  በ“መ ኢ አ ድ” ድርጅት ላይ ያነጣጠረ ስድብ እና የማንኳሰስ ዘለፋ/ፕሮፓጋንዳ ልብ ይለዋል።  ስድብ ብቻ ሳይሆን  “መኢአድ” የተባለ ድርጅት “ሞቶ የተቀበረ” እና በመሬት ላይ የሌለ ድርጅት እንደሆነ የኢሳትን ፕሮፓጋንዲስቶች ጥላቻቸውን ላመስተላለፍ ጣቢያውን ይጠቀሙበታል።
ESAT's Mulugeta Lule

ደሞዝ የማይከፈላቸው “ነፃ አገልግሎት ሰጪ ጋዜጠኞች” የሚያካሂዱት የቴ.ቪዥን ድርጅት ነው እየተባለ በኢትዮጵያ ሉአላዊ ክብር ማለትም በሰንደቃላማችን ላይ ያነጣጠረ የተቀነባበረ ዘመቻ ከጠላቶች ከኦነጐች ጋር አብረው ያጧጥፉታል። የአማራ እናቶች፤አዛውንቶች፤ህፃናት፤እርጉዞችና ዓይነስውራን ሲጨፈጨፉ፤የሴት ጡት እና የወንድ ብልት በቢላዋ እየተቆረጠ የሙታኖቹ ሬሳ አፍ ላይ እንዲጎርሰው ሲደረግ በሙታኖቹ መቃብር ላይ የተውለበለበ የፋሺስቱ የኦነግ ባንዴራ መሆኑን በዚህ ጣቢያ ውስጥ የተደራጁ ትላልቅ ጋዜጠኞች ከማንኛችንም በላይ ያውቃሉ። ሆኖም ኢሳት ቴሌቪዥን ሆን ብሎ ሌት ተቀን ከዚህ ጸረ አማራ እና ፀረ ኢትዮጵያ የጠላት ባንዴራ ጋር ፍቅር ይዟቸዋልና የሚያውለበልቡትን ርካሽ ቅስቀሳ ሁሉም አገር ወዳድ ዜጋ ሳይታክት ፕሮፓጋንዳውን እንድያከሽፍ አድካሚ እና ፈታኝ ትግል እየደቀኑብን እነደሆነ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንድታውቁት አስገነዝባለሁ።
በዚች የጠላት ባንዴራ የተገደሉ የሙታን እና አካለስንኩላን ቤተሰቦች የኦነግ ባንዴራ በኢሳት ጣቢያ በክብር ሲውለበለብ ሲመለከለቱ ምን ዓይነት የመረረ ሃዘን እንደሚሰማቸው የኢሳት ጋዜጠኞች ያውም ትላልቅ ጋዜጠኞች የሚባሉት እነ “ሙሉጌታ ሉሌ” እና “አገር ወዳድ የሚባለው “ታማኝ በየነ”  አያውቁም ብልን ለማማን ያስቸግረናል። ሆኖም የደከመ ሕብረተሰብ በላዩ ላይ ቢጨፈርበት የት ይደርሳል ከሚል ስሜት ከሆነ በጣም የተሳሳተ ትምክሕት እንደሆነ ከወዲሁ የመረጡበት ጎዳና እንዲያስተካክሉ በድጋሚ የዚህ ድረገጽ አዘጋጅ ደጋግሞ ያስገነዝባል። የማን አለኝነቱን እና “የፔቲ ቡርዣ ቡድናዊ ትምክህታቸው” በእንዲህ ከቀጠሉ በቀላሉ ያዝ ለቀቅ የምናደርገው የፖለቲካ ጨዋታ እንዳልሆነ እንዲያውቁት እፈልጋለሁ። በዚህ ሴራ የተካፈሉ ግለሰዎች በመጽሐፍ መልክ ስማቸው ተጽፎ ለታሪክ እንዳይቀር ጥንቃቄ ያድርጉ። ወያኔን የሚያከል ክፉ ጠላት የመታገሉ ልመንዱም ቁርጠኛነቱም ስላለን እንኚህ ወዳጆቻችንም በቀላሉ የምንምበረከክ ቀጤማዎች አንዳልሆንን “በፔቲ ቡርዣ ሕሊና እየሰከረ ያለው ኤሊቱ ክፍል” እንዲያውቁልን እናሳስባለን።
ኦነግም ሆነ ዓረብ ነኝ የሚለው ቅዠታሙ “የኦጋዴኑ ጂሓዲስታዊ እስላም” ወደ ተቃዋሚ ፖለቲካ ጐራ “ተቀላቀሉ፤አልተቀላቀሉ  መጡ፤ አልመጡ” “የዓይን ብሌናችን” የሚባሉት የኢትዮጵያን ብሔራዊ ቋንቋ፤ድምበር እና ዓለም በመላ ያወቀው ብሔራዊ የኢትዮጵያ ሰንደቃላማችንን ካላከበረ ለኔ “ኢሚነት ነው”። ኢምንት ብቻ ሳይሆን እሴቶቻችንን/ሉአላዊነታችንን የማያከብሩ  “ጠላቶች ናቸው”።ሉአላዊነታችን ለፖለቲካ ገበያ ለድርድር አናቀርብም። ሁላችንም የዚች መሬት ልጆች ነን እና አንዱ በሌለው የሚያሰየው የፖለቲካ ማስፈራሪያ ባንዴራ በማሳየት የሚያስፈራሩንን መንገድ ያቁም! ጉዳት ከመጣ አማራው ወይንም ትግሬው ብቻ ሳይሆን የባእድ ባንዴራ አውለብለቢዎችም ተጐጂ መሆናቸው ካሁኑኑ ማወቅ ይኖርባቸዋል።
ይህ ሉአላዊነትን የሚጻረር የኦነጐች ባንዴራ የማውለብለብ እና የመቀበል ድርጊት በኢሳት እና ጉንቦት 7 በሚደግፉ ተቃዋሚ ድረገፆች ላይ በተደጋጋሚ ለኦነግ ተባባሪነታቸውን አሳይተዋል። በነሱ ብቻ ሳይወሰን ያገራችንን ሉአላዊ ሰንደቃላማ “ኦነግ” ከሚባለው ያልታወቀ አገር ባንዴራ ጋር ካልተውለበለበ “ የኢትዮጵያ ሰንደቃላማም አዳራሽ ስብሰባ ውስጥ ለሕዝብ አይውለበለብም፤ ተብሎ በሲያትል ሕዝባዊ ስብሰባ አዘጋጆች እንደተፈጸመ ድርጊቱ በወቅቱ አውግዘነዋል። ዛሬም ይህ ድርጊት ኢሳት የተባለው ጣቢያ አጉል የፖለቲካ ትርፍ ለማራመድ ሲል ተመሳሳይ ዘመቻና ድፈርት እያካሄደ ነው። ኦነግን የሚያክል  የአገራችን ሉአላዊ ምልክቶች የማያከብር ድርጅት “ጤነኛ ነው” ብሎ ክብር መስጠት “የጠላት መጋሪያ” መሆን ነው (መጋሪያ በትግርኛ  አማርኛው “የመገልገያ ዕቃ” ማለት ነው)።
የኢሳቱ ጋዜጠኛ መሳይ የተባለው ወጣት ከኤርትራ መውጣት የማይፈቀድለትን የሻዕቢያ አማካሪ የሆነው የቁም እስረኛ ብ/ጀኔራል ከማል ገልቹ  ከአስመራ በስልክ ጋብዞ ወደ ቴ/ቪዢኑ በመጥራት በቅርቡ በደቡብ ኢትዮጵያ “ጉርዳ ፋርዳ” ከተባለው አካባቢ ስለተባረሩት አማራዎች አስመልክቶ እንዲያብራራለት http://www.youtube.com/watch?v=cN1TFurIc7s&feature=player_embedded
ሲጠየይቀው “በጣቢያው ላይ ጸረ ኢትዮጵያዊነት እና ጸረ አማራ ባንዴራ” የሆነቺው የኦነጐች ባንዴራ “ሆን ብሎ” እንዲውለበለብ ሕጋዊ እውቅና መስጠቱ ብቻ ሳይሆን የገረመን፤
“ይሄ ተግባር (አማራን የማባረርና የመግደል) በደቡብ ኢትዮጵያ የተፈጸመው ለመጀመሪያ ጊዜ ሳይሆን ካሁን በፊት በተለያ ጊዜ በተለያ አካባቢ ተፈጽሟል።ይሄ ልዩ የሚያደርገው ግን፤ በጣም ልዩ የሆነ ሁኔታ የሚያደርገው ልዩ የፖለቲካ ብቀላ ያለበት ትልቅ የሕዝብ ጥላቻ የተንጸባረቀበት እና  በተለይም በጣም አሳዛኝ የሆኑ እህቶቻችን እናቶቻችን በስነ ስርአቱ ተንከባክቦ መቀመጥና ማኖር ሲገባቸው፤ከምን ጊዜም በላይ የተዋረዱበት አሳዛኝ ድርጊት ነው
በማለት ከማል ገልቹ ሲገልጽ የኢሳት ጋዜጠኛው መሳይ ግን  ” ካሁን በፊት ከዚህ በባሰ ሁኔታ የፖለቲካ ብቀላ ያለበት በአማራ ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ከማል የነበረበት ድርጅትና አሁንም እያውለበለበው ያለው ባንዴራ በኦነግ የተፈመው ወንጀል ለምን እንዲያብራራለት እንዳልጠየቀው በተንኮል ሆን ተብሎ አንዳይጠይቀው እንደተደረገ ማወቅ አስቸጋሪ አይሆንም።” የተለያዩ መረጃዎችን እያመሳከርን የጣቢያው ተደጋጋሚ እና ቀጣይ ባሕሪው ስንገመግመው ይህ ጣቢያ ድርጅታዊ እና ፖለቲካዊ ስራ ለማሰራጨት የተዋቀረ ጣቢያ መሆኑን ያመላክታል።እውን የጣቢያው አዘጋጆች/ሃላፊዎች “ወያኔ እና ኦነግ” በሰሩት ወንጀል ኦነግን ንፁህ ወያኔን ብቻ ግን ወንጀለኛ የማድረጉን ሞራልና መብት ከየት እንዳገኙት ይገርመኛል? ከማል ገልቹ ሲጠይቁት በቲቪው የመስኮት ገጽታ “ስክሪን” ላይ “የኦነግ ባንዴራ ማውለብለብ፤ ማስጠጋት ማራቅ ማድመቅ፤ማጀብ፤ማሳጀብ” ምን አመጣው? ምንስ ለማለት ነው? በኦነግ ባንዴራ ካልታጀበ የከማል ገልቹ ፎቶ ብቻ ማሳየት ለዓይን ማራኪ አይሆንም ነው? በጣም ይገርማል!    
ከማል ገልቹ ደጋግሞ “ሕዝብ” እያለ የተጠቀመው ቃል  “አማራ” መሆኑን “የተፈጸመው ፖለቲካ ብቀላ”  የሚለው ደግሞ “የጎሳ/የዘር ጥላቻ” እንጂ “የፖለቲካ ብቀላ”  አለመሆኑ ለጣቢያውም ሆነ ለከማል ገልቹ ላስገነዝባቸው እወዳለሁ። “ካሁን በፊት እንዲህ ያለ የከፋ ድርጊት በሕዝብ (በአማራው ላይ) ላይ የከፋ ድርጊት አልታየም “ ሲል የጎሳ ብቀላ መነሻ ያደረገ የኦነግ ወንጀል ለማድበስበስ እና ለማሳነስ ቢሞክርም በፊት በተለያዩ ቦታዎች አማራዎች ከኦሮሞ አካባቢ ውጡ ሲባሉ እና ሲጨፈጨፉ ኦነግ ስለፈጸመው ተመሳሳይ ብቻ ሳይሆን የከፋ  የጭፍጨፋ እና የማባረር “የዘር ማጥፋት” ወንጀል እንደፈጸመ ጋዜጠኛው  “ሳይጠይቀው” ለምን በቸልታ አለፈው? ኢሳት እና ነፃ ነን የሚሉት ሚዲያዎች በኦነግ ነብሰገዳዮች በአማራው ሕብረተሰብ ላይ የደረሰው የዘር ማጥፋት ጥቃት እየተከታተሉ ካላጋለጡ እና መላው ዓለም እንዲያውቀውና “ኢትዮጵያ  ሕዝብም” እንዲያውቀው ካላደረጉ ለአማራው ማን ነው የሚጮህለት? ወያኔ ወይስ ኦነግ ነው ስለ አማራው ማለቅ፤መጠቃት የሚጮሁለት? አንገታቸው እንደ ደሮ የተቀነጠሱት ህጻናት እና አማራን ንተከላክላችሗል ተብለው የታረዱ ኦሮሞዎች ደም ይወቅሰናል ብላችሁ ትንሽ አታፈሩም? 
ኢሳት የጋዜጠኛ ጀማሪዎች መጫወቻ እና መለማመጃ ለምን ተደረገ? ካሁን በፊት ግንቦት 7 የተባለው የራዲዮኑ አዘጋጅ አማራውን ያስጨፈጨፈው አረመኔው “ሌንጮ ለታ” ጋብዞ “ክቡር አቶ ሌንጮ  ሕዝባችን እንደ እርስዎ የመሰለ “ሰብአዊነት” የተላበሰ መሪ ያስፈልገዋል ” ብሎ ሲያሞግሰው ስሰማ “የጋዜጠኛነት ብቻ ሳይሆን የአገራቸውን ፖለቲካ በቅጡ ያልተከታተሉ አዳዲስ ወጣቶችን በነፃ አገልግሎት ስም በመቅጠር “ወንጀለኞችን” ሰብአዊነት የተላበሱ ናቸው እያሉ የተሳሳተ መረጃ ወደ ሕዝብ ሲያረጩ (የድርጅቱ ሃላፊዎች አለማቸው ስለሆነ ከነ ብርሃኑ እና አንዳርጋቸው መሳይ አዘጋጂውን ያርሙታል ተብሎ አይገመትም) የሚያርማቸው ክፍል ወይንም ጣቢያውን የሚያወግዝ ምሁር ግን አላየሁም።ለምን? ሙሶሎኒ ወይንም መለስ ዜናዊ ወይንም ኢሳያስን፤ሂትለርን፤መንግስቱን…..“ ሰብአዊነት የተላበሳችሁ ናችሁ” ብሎ ሲላቸው ውሸት የሚያሰራጭ ሚዲያ ስታደምጡ ምን ይሰማችሗል?
‘ኢሳትም”  የኦነግ “መጋሪያ”  ሆኖ እያስተጋባለት ያለው የውሸት ስራ ስንገመግመው እነዚህ ከዚህም ከዚያም የተጠረቃቀሙ ነፃ አግልግሎት ሰጪ ጋዜጠኞች “አብዛኞቹ” (ጥቂቶች ልምድ ያለቸውና የበሰሉትን ወደ ጎን ትተን) ብስለት ስለሌላቸው  ጊዚያዊ ፖለቲካ ለማራገብ ሲሉ በሕዝብ ላይ የውሸት ምስል ለመቅረጽ እየሞከሩ ስለሆነ ጣቢያው ውስጥ “ሉአላዊነታችንን እንንከባከባለን” የሚሉ አገር ወዳዶች  ካሉ እንዲያስቡበት ምክር እለግሳለሁ።
ለጊዚያዊ ማታለያ እና ርካሽ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ሲባል የአገር ሰንደቃላማ እና ክብር እንዲሁም የተፈጸሙ ወንጀሎች እንዳልተፈጸሙ እየሸፋፈኑ የሌሎችን ወንጀሎች ለማጉላት ቆሻሻ ጋዜጠኛነት ስራ መስራት ግለሰቦችን ወይንም ድርጅትን ሳይሆን “የተበደሉ ሰዎችን” ዋጋ አለመስጠት ከባድ የጋዜጠኛነት ከፍተት እና ወንጀልም ነው።
ይህ የኢሳት ወዳጅ የሆነው ኦነግ የተባለው የከማል ገልቹ ድርጅት በኤፕሪል 11/2014 ላይ በንቺ ማጂ/ጉራ ፋርዳ ስለተባረሩት አማራዎች አስመለክቶ “ወያኔን” የሚኰንን ድርጅታዊ መግለጫ አውጥቷል።በጣም የሚገርመው ነገር በወዳጁ በኢትዮሚዲያ ድረገጽ ላይ የተለጠፈው መገልጫው ላይ የተጠቀመው ባንዴራና አርማው ቋንቋዎችም የሚመለከት ዛሬም “ጸረ ኢትዮጵያነቱን” የሚያረጋግጥ “ርካሽ” እና ጸረ-ሉአላዊነታችን የሆነ ድርጅት መሆኑን በማያከራክር መረጃ ለማየት አስችሎናል።
ድርጅቱ የተጠቀመው የመገልጫ ቋንቋ እንግሊዚኛ እና አረብኛ” ነው። ማህተሙም  አማራ ሲጨፈጨፍ የተውለበለበቺው የኦነግ ባንዴራ እና አርማ ነው። እንግዲህ ልብ እንድትሉት የማስገነዝበው፡ “ወደ ልቡ” ተመልሷል፤ኢትዮጵያዊነትን እና ሉአላዊነትን አስከብሯል” እያሉ ኢሳቶች እና መሰል ጉድፍ ፖለቲካ ድርጅቶች የሚዋሹን ስታገናዝቡት “አሁንም ኦነግ ከስሕተቱ/ከወንጀሉ እንዳልተጸጸተ እና እንዳልተማረ ነው።
ለዓረብኛ (የአረቦች) ቋንቋ እና ለኤውሮጳዊያን (ለላቲኖች) ቋንቋ ለቅኝ ገዢዎች ፊደል እና ቋንቋ ፍቅር ላደረባቸው ሰዎች የባዕድ ፊደልና ቋንቋ ባህላችን እና ቋንቋችን ነው ብለው መግለጫ ቢያወጡ የራሳቸው ጉዳይ ነው። ነገር ግን ለእኛ ለኢትዮጵያዊያን በተለይም ለተጠቃው ለአማራው በሚያነበው እና በሚረዳው በቋንቋው በአገሩ በአማርኛ ቋንቋ ጽፈው መባረረን እና ግድያን የደረሰባቸው ወገኖቻችን የሃዘናቸው ተካፋይ መሆናቸውን በአማርኛ ቋንቋ መግለጹ ለእነ ከማል ገልቹ የከበዳቸው ነገር ምንድ ነው?  አማርኛ መጻፍ አያውቁም? ካላወቁ ለወዳጃቸው ለትግል አጋራቸው ለንአምን ዘለቀ ወይንም ለብርሃኑ ነጋ ድርጅት አስተርጉሙልን ብለው አስፅፈው ማውጣት ምን ከበዳቸው?
ካሁን በፊት ሌንጮ የተባለው “አረመኔ” ኢሳት ላይ ቀርቦ ጋዜጠኛው “ፋሲል የኔሰው” በአማርኛ ሲጠይቀው ሌንጮ “አማራ እና አማርኛ” ስለሚጠላ ሲመልስለት የነበረው “በእንግሊዝኛ” ቋንቋ ነበር። የህ በሽታ የተማሩት ከመምህራቸው ከኢሳያስ አፈወርቅ ነው። 
በነገራችን ላይ ፡ የሻዕቢያው መሪ ኢሳያስ አፈውርቂ “መለስ ዜናዊና መንግስቱ ሃይለማርያም” ባገር ወዳድንት ሲያወዳድራቸው (ዋሺንገተን ስብሰባ ላይ የተናገረው ነው- አሁን የምሰጣችሁ ታሪክ የማወራችሁ መረጃ ቪዲዮው አለኝ) እንዲህ ይላል “ምንም እንኳ መንግስቱ ‘ቆዳው /ሐረሮ/ (አስጠሊታ የሆነ የተቃጠለ የቆዳ ቀለም ማለቱ ነው “ሐረሮ” ሲል ) ቢሆንም  እና ከንፈሩም ‘ምንጭራም’ (የተለጠጠ ወፍራም)  ይሁን እንጂ መንግስቱ አገር ወዳድ ነው፡ መለስ ግን አገራዊ ስሜት የለውም።” ሲል ዘረኛ ባሕሪው ሳያፍር ሲናገር  በእንግሊዝኛ ካልመለሱና ካልጻፉ መነሻ ግባቸው የተዋረደ መስሎ ስለሚሰማቸው በባእድ ፊደል እና ቋንቋ መጻፍን ይመርጣሉ።
ኦነግም “የድርጅቱ መግለጫ” በብሔራዊ ቋንቋችን በሚገባን ፉደልና ቋንቋ ጽፎ ቢያስነብበበን ምን የፖለቲካ ኪሳራ ይገጥመኛል በሎ ነው? (ያውም ወደ ኢትዮጵያዊነቱ አንድ ግማሽ መንገድ ያስጠጋዋል እንጂ)።በአገራችን ሰንደቃላማ/አርማ እና በገዛ የራሳችን በብሔራዊ ቋንቋችን በአማርኛ እና በግዕዝ ፊደል አስፍረው፤አትመው እንድናነበው ቢያደርጉ ኖሮ “እውነትም ወደ ልባቸው ተመልሰዋል” “መገንጠልን እና አገራዊ ሉአላዊነትን ተቀብለዋል” እንል ነበር። ነገር ግን አለመታደል ሆኖ ዛሬም አማርኛ ፊደል እጅግ አድርገው ስለሚጠየፉትና የባዕድ ፊደል ስለሚሉት ከማል ገልቹ ዛሬም በመግለጫው ላይ “በዓረብኛና በእንግሊዚኛ፤እንዲሁም ፈረንጆች የሰጧቸውን ‘ቁቤ’ የተባለው ላቲን ኦሮሚኛ ጽሑፍ ያለበትን ማሕተም/ሎጎ ” በኢትዮ ሚዲያ ማውጣቱን ዛሬም ቀጥሎበታል።
እሱ ብቻ ሳይሆን ከማል ገልቹ አራሱ “ብሔር፤ብሔረሰቦች፤ሕዝቦች” ምን ማለት እንደሆነ እና ምንጩ እና ከየት እንደተገኘ ተንትኖ ማስረዳት የማይችለው ምስኪኑ “ከማል ገልቹ” ወያኔ ያስተማረው “ብሔር ፤ብሔረሰብ እና ሕዝቦች” የሚለው ምን ትርጉም እንዳለው የማይታወቅ የጣሊያን ፋሺስቶች ቅዠት ዛሬም ልክ እንደ “ወያኔ” በተለጠፈው መግለጫው ላይ ደጋግሞ ተጠቅሞበታል (በኢሳት በቃለ መጠይቁም እንዲሁ) ። ይህ ነው እነ “ኢሳቶች” እና  “ግንቦቴዎች” ስለ ኦነጋቸው “ኢትዮጵያዊነት” እየደጋጋሙ በቴ/ቪዥናቸው እና ራዲዮናቸው ባንዴራቸውን እያውለበለቡ የወያኔ “ብሔር’ብሔረሰብ፤ሕዝቦች” እያሉ “የህፃናት ጨዋታ” (የፕሮፈሰር መስፍን ወልደማርያም ቃል አጠቃቀም ልዋስ እና )ጨዋታቸውን እስኪያቅለሸልሸን ድረስ እያስደመጡን ያሉት።የኢሳት  የራዲዮንና የቲቪው ጋዜጠኛም “ብሔር፤ብሐረሰብ፤ሕዝቦች” ስትል ምን ማለት ነው ብሎ ከማል ገልቹን መጠየቅ ሲገባው ከማል ገልቹ የሚያክል አዲስ የኢሳት ጣቢያ የፖለቲካ ተንታኝ ሳይጠይቀው አልፎታል። ለምን?
 “የፈረንጅ ሚዲያም ቢሆን የአልቃይዳም ባንዴራ እንኳ ሳይቀር  በእስክሪን ላይ እንዲታይ ያደርጋል” እና ኢሳትም “ እንቁራሪት ይደረጋል ብላ ተተኩሳ ሞተች” የሚባለው የፈረንጅ ቅጅ ቀድቶ “አማራን የጨፈጨፈች ባንዴራ እና የወደፊቷ ኦሮሚያ ሪፑብሊክ የተባለ አገር ስትመሰረት የምትሰቀል ባንዴራ“ በቲቪ እስክሪኑ ላይ  እስኪያቅለሸልሸን ድረስ በልዩ ልዩ “ሞሺን ግራፊክስ” አቀራረብ እያውለበለቡ ሕዝብን ማሳሳት ጸረ አንድነት እና የማንንት እሴቶች/ሉአላዊ ምልክቶቻችን ክብር የሚጻረር ስለሆነ እኛ ኢትዮጵያዊያን  እንኮንነዋለን።ኢሳት ቲቪ ወገናዊነት እያጠቃው እንደነበረ የጣቢያው አፈኛ አቶ አበበ በለው ካሁን በፊት በሕዝብ ፊት በኑዛዜ ማመኑን የሚያስመሰግነው ቢሆንም፡  ዛሬም ቢሆን ኢሳት ቴ/ቪዥን ጣቢያ  ከዚያ ስህተቱ ሳይታረም ለኦነግ በመወገን  ሉአላዊነትን የሚጻረሩ እሴቶችን በለዘብተኛነት በጣቢያው ላይ እያስተላለፈ ክፉ መንገድ እየጠረገልን ነው።፡ ስለሆነም ኢሳት ቴ/ቪዥን “ፓን” ኦሮሚያ እና “ፓን” ኢትየጵያዊነትን ማምታታቱን ያቁም!”

አገር ውስጥ ያለው ሕዝባችንም ኢሳት የተባለው  ጣቢያ “የጠላቶች መጋሪያ” መሆኑን እንዲያቆም መልእክት እንዲያስተላልፍለት ጥሪየን አስተላልፋለሁ። “የጠባብ ቡድኖች” የፕሮፓጋንዳ ማሰራጫ ሃይል እየሆነ እንደመጣ ብዙ መረጃዎችን ማቅረብ ይቻላል። ከነዚህ ጥቂቶቹን መረጃዎችን እነሆ ያንብቡ፡A deliberate and outright deception--part I Part II Part III by Dr.Mankelkilot Haileselassie  http://www.ethiolion.com/article/040612_A_deliberate_and_outright_deception.html

ጌታቸው ረዳ
 ኢትዮጵያን ሰማይ ድረ ገጽ አዘጋጅ
 ሳንሆዘ ካሊፎርኒያ - አሜሪካ።