Tuesday, January 27, 2009

የወያኔዉ ሜጀር ጀነራል አበበ ተክለሃይማኖት እና

የወያኔዉ ሜጀር ጀነራል አበበ ተክለሃይማኖት እና የዓረናዉ ፓርቲ ምክትል መሪ አዉዓሎም ወልዱ የተሳተፉበት ወንጀል ከጌታቸዉ ረዳ ክቡራን የኢትዮጵያ ሰማይ ብሎግ አንባቢዎች፡ ወያኔ የተባለዉ ድርጅትን በከፍተኛ ስልጣን ሲመሩ ኖረዉ በተለያዩ ምክንያቶች ከድርጅቱ የተሰናበቱ እና የተቀሩትም ድርጅቱን በመምራት ላይ የሚገኙ መሪዎች ቀደም ብየ ለብዙ አመታት መቃወሜ ግልጽ ነዉ። የእነዚህ አረመኔ ግለሰቦቹን ማንነት ሳያዉቁ የወያኔ አጨብጫቢዎች በመሆን ግማሾቹ በአምባሳደርንት ግማሾቹ በገንዘብ አዋጪነት ፤ከፊሎቹ በየፓልቶኩ ላንቃቸዉ አስኪደርቅ በስሜት ስለወያኔ ቅዱሳን ሃዋርያትነት በመስበክ ለብዙ ኣመታት ራሳቸዉን ሲያሞኙ ታዝበናቸዋል። እነኚህ ደጋፊዎቻቸዉ ለምን እንደሚደግፉዋቸዉ የተለያዩ ራሳቸዉ ምክንያቶች አሉዋቸዉ። አባት እናት ወንድሞቻቸዉ ገድሎዉባቸዉም “በ ባሪያነት ሙሉ መንፈሳቸዉ ለማገልግል ፈቀደኞች የሆኑ በተለያዩ ምክንያቶች ራሳቸዉን ለወያኔ ሸጠዉ ለማገልገል ያደሩ የዋህ “ዕዉራን ንቦች”በየቦታዉ እንዳሉዋቸዉ የምታዉቁት ጉዳይ ነዉ። በንቅዘት የተበከሉ ወንጀለኞች እና ባንዳዎች የሚመሩት ይህ ድርጅት ለምን እነደሚከተሉት ይየተለያየ ምክንያታቸዉ ያፈለገዉ ይሁን፤ መሪዎቻቸዉ ከሰሩት ወንጀል እና ሰብኣዊ ጥሰት ተጠያቂነት ሊከላከሉላቸዉ የተቻላቸዉን ያህል ታች እና ላይ ቢሉም ፤ከቶዉንም ታሪክ የዘገበዉ አረመኔ የገበና የወንጀል ማህደራቸዉ ሊከዉሏቸዉ ግን አይቻላቸዉም። በቅርቡ የወያኔዉ የአየር ሃይል ኮማንደር/አዛዥ የነበረዉ ጀኔራል አበበ ተክለሃይማኖት (ጆቤ) በረሃ ዉስጥ የወንጀለኛዉ የወያኔ ድርጅት ታጋይ ሆኖ ትግራይ ዉስጥ በሽሬ አዉራጃ በረሃዎች የወያኔ እስር ቤት (ባዶ ሽድሽተ-06) ሃላፊ ሆኖ ተመድቦ ሲሰራ ገበሬዎች ፣ የከተማ ወጣቶች እና አዛዉንት ኗሪዎች በእሳት እየለበለበ ያሰቃያቸዉ የወንጀል ድርጊቶቹ እና በወቅቱ አብሮት ከእርሱ ጋር የነበረዉ የኤርትራ አምባሳደር ሆኖ በወያኔ ተሹሞ የነበረዉ ከመለስ ጋር ከተጣሉ በሗላ ደግሞ የገብሩ አስራት ምክትል የድርጅት ሃላፊ ሆኖ “ዓረና ትግራይ” የተባለዉ ሌላ ብሄረተኛ ቡድን በመምራት ላይ የሚገኘዉ የበረሃ ስሙ “አዉዓሎም ወልዱ” ትከክልኛ ስሙ “ትኩእ ወልዱ” አስረኞችን ከተቀፈደዱበት አስር ቤት እያስወጣ ስም ዝርዝር በመጥራት አስረኞቹን ተሰናበቷቸዉ እያለ በግፍ በመረሸን የሰሩትን ወንጀል ለሕዝብ ይፋ ስለሚሆን እንድትከታተሉን ስናሳስብ፡ በትግራይ ሕዝብ ላይ የተለያዩ ሰብኣዊ ግፎችን ፈጽመዉ ስማቸዉ ለጊዜዉ ለማዉጣት ባለን ምክንየት የተያዙ ስም ዝርዝሮች ስላሉ፤ የሕግ ባለሞያዎችን እስክንፈልግ ድረስ በትዕግስት እንድትከታተሉን ኣሳስባለሁ። በወላጆቻችን ደም ቀልደዉ ሞኞችን ቢአሞኙም “ዛሬ በስመ ዲሞክራሲ እና በብሄረተኝነት”መጋረጃ መደበቅ ለጊዜዉ እንጂ ከታሪክ ግን መደበቅ ከቶ ኣይቻልም። ጌታቸዉ ረዳ የኢትዮጵያ ሰማይ የህዋ ሰሌዳ አዘጋጅ